“70 ደሜ ነው ሌላው ትርፍ ነው።”
የአንበሶቹ ስብስብ የአምናው ሻምፒዮና መቐለ 70 እንደርታ ኘሪምየር ሊጉን ከተቀላቀለበት 2010 ዓ/ም አንስቶ ባሳለፍነው ሳምንት ሰበታ ከነማን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት እስከረታበት 9ኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ መርሃ ግብር 69 ጨዋታዎች ያደረገ ሲሆን 37 ጨዋታዎች አሸንፎ 16 ጨዋታዎች ተሸንፎ 16 ጨዋታዎች በአቻ ውጤት ተለያይቷል። በነዚህ 69 ጨዋታዎች 85 ጊዜ ኳስና መረብ ሲያገናኝ 49 ጎሎች ተቆጥረውበታል።መቐለ 70 እንደርታ በሜዳው ካደረጋቸው 35 ጨዋታዎች 2 ጊዜ ብቻ የተሸነፈ ሲሆን በ69 የፕሪሚየር ሊጉ ጨዋታዎች በአማካኝ በየጨዋታው 1.23 ጎሎች ማስቆጠር ችሏል።መቐለ 70 እንደርታ የፊታችን ቅዳሜ ወደ ዲቻ አምርቶ ወላይታ ዲቻን ሲገጥም የፕሪሚየር ሊጉን 70ኛ ጨዋታው የሚያደርግ ሲሆን ይህ ቁጥር ከመለያው ጀርባ ተሸክሞ በልቡ ውስጥ
አትሞ ክለቡን ለሚደግፍ ደጋፊ ልዩ ትርጉም አለው።70 የሆነው በምክንያት ነውና ቀኑ ድል የምናደርግበት መሆኑን ስገልፅ በልበ ሙሉነት ነው።
“70 ደሜ ነው ሌላው ትርፍ ነው”
ashu mk fan
©የቡናውያን ዘር ሐረግ
ኽብሪ ልግበኦም ጀጋኑ ደገፍቲ ኣብ ሆሳዕና
የመቐለ 70 እንደርታ የ15 ጨዋታዎች ግስጋሴ ቁጥራዊ መረጃ
⛳️15 – ተጫወተ
💪8 – አሸነፈ
🤝1 – አቻ
❌6 – ተሸነፈ
⚽️20 – አስቆጠረ
⚽️15 – ተቆጠረበት
👉 ባጠቃላይ መቐለ 70 እንደርታ ከ15 ጨዋታዎች 25 ነጥብ (+5 የጎል ክፍያ ⚽) በመሰብሰብ የመጀመርያው ዙር ቅዱስ ጊዮርጊስን እና ፋሲል ከነማ ተከትሎ በ3ኛነት አጠናቋል።
ዝርዝር ጨዋታዎች
1ኛ ሳምንት- መቐለ 2-1 ሃድያ ሆሳዕና
2ኛ ሳምንት- ባህርዳር 3-2 መቐለ
3ኛ ሳምንት- መቐለ 1-1 ኢትዮጵያ ቡና
4ኛ ሳምንት- ሲዳማ 1-2 መቐለ
5ኛ ሳምንት- መቐለ 1-0 ወልዋሎ
6ኛ ሳምንት- ቅ/ጊዮርጊስ 2-1 መቐለ
7ኛ ሳምንት- መቐለ 2-0 ኣዳማ
8ኛ ሳምንት- ወልቂጤ 0-1 መቐለ
9ኛ ሳምንት- መቐለ 2-1 ሰበታ ከተማ
10ኛ ሳምንት- ወላይታ ድቻ 1-0 መቐለ
11ኛ ሳምንት- መቐለ 1-0 ስሑል ሽረ
12ኛ ሳምንት- ጅማ 1-0 መቐለ
13ኛ ሳምንት- መቐለ 0-2 ፋሲል
14ኛ ሳምንት- መቐለ 5-1 ሃዋሳ
15ኛ ሳምንት- ድሬዳዋ 1-0 መቐለ
“70 ደሜ ነው ሌላው ትርፍ ነው።”
@ashumkfan
ወደ ፍቅር ጉዞ 70ን ይዞ!
የሰሜኑ ኮከብ ከምስራቁ ኮከብ የሚያገናኘው የመጀመርያው ዙር የመጨረሻ ሳምንት ጨዋታ በፍቅር ከተማዋ ድሬ የካቲት 15/2012 ይካሄዳል። ሻምፒዮናው ክለባችን ከአስደሳች የሜዳ ላይ ጣፋጭ ድል ወደ ድሬ የሚጓዝ ሲሆን ድሬ በአንፃሩ ከሽንፈት በኋላ የሚያደርጉት ጨዋታ ነው።ሁለቱም ክለቦች ከ2010 ጀምሮ 4 ጊዜ ሲገናኙ መቐለ 70 እንደርታ 2ጊዜ በሜዳው 1ጊዜ ከሜዳው ውጪ ባጠቃላይ 3ጊዜ ሲያሸንፍ (2ለ0፥2ለ1፥2ለ1) ድሬዎች 1ጊዜ ብቻ (1ለ0) በሜዳቸው ድል ቀንቷቸዋል። መቐለዎች 6 ግቦች ስያስቆጥሩ ድሬዎች 3 ግቦችን አስቆጥረዋል።ሁለቱም ክለቦች ዘንድሮ ለ5ኛ ጊዜ የሚገናኙ ሲሆን ድሬዎች ከወራጅ ቀጠና ለመውጣት መቐለዎች ወደ መሪነት ለመመለስ የሚያደርጉት ጨዋታ በመሆኑ ጨዋታው ከወዲሁ አጓጊና ተጠባቂ አድርጎታል።
ድል ለተወዳጁ ክለቤ
70 የሆንኩት በምክንያት ነው
#ashu mk fan
አንበሶቹ ወደ ድል የሚመለሱበት ቀን!
ድል ያለ ድል መቼም ለማልደራደርበት 70 እንደርታ
“70 ደሜ ነው ሌላው ትርፍ ነው”
@ ashu mk fan
ጀግናችን እንኳን ተወለድክልን
ተጠባቂው የሰሜኑ ደርቢ ማን ያሸንፍ ይሆን???
ድል ያለ ድል መቼም ለማልደራደርበት 70 እንደርታ
“70 ደሜ ነው ሌላው ትርፍ ነው”
@ ashu mk fan
የሻምፒዮኖቹ ፍጥጫ
12ኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ጨዋታ የ2ቱም ዓመታት ሻምፒዮኖች ያገናኛል።የ2010 ሻምፒዮን ከ 2011 ሻምፕዮን የሚያገናኘው የእሁድ ጥር 24/2012 የፕሪምየር ሊጉ ተጠባቂ ጨዋታ ጅፋራውያን ከ ዬሀንሳውያን ያገናኛል። ሁለቱም ክለቦች ወደ ፕሪምየር ሊጉ ካደጉበት 2010 ጀምሮ በነበሩ 2 ዓመታት ጅማ በመጣበት ዓመት 1ኛው ዋንጫ ሲያነሳ መቐለ 70 እንደርታ የአምናውን ዋንጫ ማንሳት ችሏል። ሁለቱም ክለቦች ዋንጫ ሲያነሱ የወቅቱ የመቐለ 70 እንደርታ አሰልጣኝ ገብረመድህን ሃይለ ቡድኖቹ በአሰልጣኝነት መርቷል።ሁለቱም ክለቦች በ2010 ሲገናኙ መቐለ 70 እንደርታ በሜዳው በያሬድ ከበደ የጭንቅላት ጎል 1 ለ 0 ሲያሸንፍ በተመሳሳይ ጅማ አባ ጅፋርም በሜዳው 1 ለ 0 መርታት ችሏል። በ2011 ሲገናኙም 70 እንደርታዎች በሜዳቸው 2 ለ 1 ሲያሸንፉ በአንፃሩ ጅማ በሜዳቸው እየመሩ ቢቆዩም 70 እንደርታዎችን ማሸነፍ ተስኗቸዋል በዚህም ምክንያት በጅብሪል እና ማውሊ ጎሎች ታግዘው መቐለዎች 2 ለ 2 በሆነ ውጤት ነጥብ ተጋርተው ወጥተዋል። ባጠቃላይ ሁለቱም ክለቦች 4 ጊዜ ተገናኝተው 70 እነደርታ 2 ጊዜ ሲያሸንፍ ጅማ 1 ጊዜ አሸንፎ 1 ጊዜ አቻ ተለያይተዋል። መቐለዎች 5 ግቦች ስያስቆጥሩ ጅፋሮች 4 ግቦችን አስቆጥረዋል።ሁለቱም ክለቦች ዘንድሮ ለ5ኛ ጊዜ የሚገናኙ ሲሆን በቀደመው ታሪካቸው ምክንያት ጨዋታው አጓጊና ተጠባቂ አድርጎታል።
ድል ለተወዳጁ ክለቤ
“70 ደሜ ነው ሌላው ትርፍ ነው”
@ ashu mk fan